languageIcon
አማርኛ
አማርኛ
العربية
Azeri
বাংলা
Bosanski
Deutsch
English
Español
Filipino
فارسي
Français
(Hausa) هَوُسَ
हिन्दी
Indonesia
italiano
Қазақ тілі
தமிழ்
كوردی
नेपाली
Português
Pусский
සිංහල‎
Gjuha shqipe
Kiswahili
ภาษาไทย
Türkçe
Українська
اردو
Yorùbá
中文
search
search
ዚክርን አስመልክቶ ከነቢዩ -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን- በሐዲሥ የተዘገቡ በርካታ ናቸው፡፡ ከእነርሱም መካከል፡-(1)

1. አቢ ሁረይራህ -አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው- እንዳስተላለፉት የአላህ መልእክተኛ -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን-፣ “አንድ መቶ ጊዜ ላ ኢላሀ ኢልለልላህ ወሕደሁ ላ ሸሪይከ ለህ ለሁልሙልኩ ወለሁልሐምዱ ወሁወ ዐላ ኩልሊ ሸይኢን ቀዲይር አስር ጫንቃዎችን ነጻ ከማውጣት ጋር ምንዳው ሲስተካከልለት አንድ መቶ ምንዳዎች ይጻፉለታል፣ አንድ መቶ ሐጢአቶችም ይሰረዩለታል፣ ይህች ቃልም በዚያ ቀን እስኪያመስ ድረስ ከሸይጣን ጥበቃ ትሆንለታለች፡፡ እሱ ከሰራው ሥራ የተሻለ ሥራ ሰርቶ ማንም አይመጣም እሱ የሰራውን ዓይነት ሥራ አብዝቶ ሰርቶ ከሚመጣ ሰው በስተቀር፡፡ በቀን ውስጥ አንድ መቶ ጊዜ ሱብሓነ-ልላህ ወልሐምዱሊልላህ ያለ ሐጢአቶቹ የባሕር አረፋ ያህል ቢሆኑም ይሰረዩለታል፡፡” ብለዋል፡፡ ቡኻሪ ሐዲሡን በሐዲሥ ዘገባ ቁጥር (3293)፣ ሙስሊም ደግሞ በቁጥር (2691) ላይ ዘግበውታል፡፡

አቢ አዩብ -አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው- እንዳስተላለፉት ነቢዩ -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን-፣ “አስር ጊዜ በመደጋገም ላ ኢላሀ ኢልለልላህ ወሕደሉ ላ ሸሪክ ለሁ ለሁልሙልኩ ወለሁልሐምዱ ወሁወ ዐላ ኩልሊ ሸይኢን ቀዲይር ያለ ከኢማዒል ልጆች አራት ነፍሶችን ነጻ እንዳደረገ ነው፡፡” ብለዋል፡፡ ቡኻሪ በሐዲሥ ዘገባ ቁጥር (6404)፣ ሙስሊም ደግሞ በቁጥር (2693) ላይ ሐዲሡን ዘግበውታል፡፡

 
Simple Audio Player
 
facebook googleplus twitter