languageIcon
አማርኛ
አማርኛ
العربية
Azeri
বাংলা
Bosanski
Deutsch
English
Español
Filipino
فارسي
Français
(Hausa) هَوُسَ
हिन्दी
Indonesia
italiano
Қазақ тілі
தமிழ்
كوردی
नेपाली
Português
Pусский
සිංහල‎
Gjuha shqipe
Kiswahili
ภาษาไทย
Türkçe
Українська
اردو
Yorùbá
中文
search
search
ደዓእን መደጋገምና በእሱም ላይ መለማመጥ

በዚህ ላይ ከዚህ በላይ ያሳለፍነው የኢብን ዐብባስ -አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው- ሐዲሥ ማስረጃ ይሆናል፡፡ በዚህ ሐዲሥ ነቢዩ -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን-፣ “አልላሁምመ አንጂዝ ሊ ማ ወዐድተኒ፣ አልላሁምመ ኣቲ ማ ወዐድተኒ፡፡ /አላህ ሆይ! ቃል የገባህልኝ ፈጽምልኝ፡፡ አላህ ሆይ! ቃል የገባህልኝን ስጠኝ፡፡” ሲሉ ከትከሻቸው ላይ ያለው ጭርቃቸው እስኪወድቅና አቡ በክር ከእሳቸው ጋር በመሆን ‹‹የአላህ ነቢይ ሆይ! ጌታህን መጠየቅህ ይብቃህ፡፡›› እሰከሚሏቸው ድረስ ጌታቸውን ከመማጸን አልታከቱም ብለዋል፡፡  ሙስሊም በሐዲሥ ዘገባ ቁጥር (1763) ላይ ዘግበውታል፡፡  

እንደዚሁ ቡኻሪና ሙስሊም ከአቢ -ሁረይራህ -አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው- በዘገቡት ሐዲሥ ላይ ነቢዩ -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን- ለዱሥ ጎሣ  ባደረጉት ዱዓእ ላይ፣ “አላህ ሆይ! የዱስ ጎሳዎችን ቀጥተኛውን መንገድ ምራቸው፡፡ አምጣቸውም፡፡አላህ ሆይ! የዱስ ጎሳዎችን ቀጥተኛውን መንገድ ምራቸው፡፡ አምጣቸውም፡፡” ብለዋል፡፡ ቡኻሪ በሐዲሥ ዘገባ ቁጥር (2937)፣ ሙስሊም በቁጥር (2524) ላይ ዘግበውታል፡፡    

እንደዚሁ በሙስሊ ትክክለኛ የሐዲሥ ዘገባ፣ “ጉዞ በሚያሰረዝም፣ ፀጉሩ የተቆጣጠረና አቧራ የለበሰ ሆኖ እጁን ወደሰማይ ዘርግቶ ጌታዬ! ጌታዬ!   ይላል፡፡” የሚል ተዘግቧል፡፡ ሙስሊም በሐዲሥ ዘገባ ቁጥር (1015) ላይ የዘገቡት ሲሆን ይህ በመደጋገም መለመን ነው፡፡

ነቢያዊ ፈለጉ ሶስት ሶስት ጊዜ ዱዓእ  ማድረጉ  ነው፡፡ ኢብን መስዑድ -አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው- ባስተላለፉትና ቡኻሪና ሙስሊም በዘገቡት ሐዲሥ፣ ‹‹ዱዓእ ሲያደርጉ ሶስት ሶስት ጊዜ ያደርጉ ነበር፡፡ ከጠየቁም ሶስት ሶስት ጊዜ ይጠይቁ ነበር፡፡ ካሉ በኋላ ሶስት ሶስት ጊዜ፣ “አልላሁምመ ዐለይከ ቢቁረይሽ፡፡ /አላህ ሆይ! በቁረይሽ ላይ ይሁንብህ፡፡/” አሉ፡፡›› የሚል ይገኝበታል፡፡ ቡኻሪ በሐዲሥ ዘገባ ቁጥር (240)፣ ሙስሊም በቁጥር (1794) ላይ ዘግበውታል፡፡ 

 

 
Simple Audio Player
 
facebook googleplus twitter