languageIcon
አማርኛ
አማርኛ
العربية
Azeri
বাংলা
Bosanski
Deutsch
English
Español
Filipino
فارسي
Français
(Hausa) هَوُسَ
हिन्दी
Indonesia
italiano
Қазақ тілі
தமிழ்
كوردی
नेपाली
Português
Pусский
සිංහල‎
Gjuha shqipe
Kiswahili
ภาษาไทย
Türkçe
Українська
اردو
Yorùbá
中文
search
search
sonnaImg
በሚመሽበት ወቅት እቃዎችን መክደንና የአላህ ስምን ማውሳት

ሲመሽ ክፍት የሆኑ እቃዎችን መክደን፣ ማጠጫዎችን ማጋደም ግጣም ካለቸውም መዝጋትና በዚህ ጊዜም የአላህን ስም ማውሳት ነቢያዊ ፈለግ ነው፡፡

ለዚህ ማሰረጃው፡- ጃቢር ኢብን ዐብዲላህ -አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው- እንዳስተላለፉት፣‹‹ የአላህ መልእክተኛ -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን-፣ “እቃን ክደኑ፡፡ ማጠጫዎችንም ግጠሙ፡፡ በአመት ውስጥ በሽታ የሚወርድበት ሌሊት አለ፡፡ ክዳን በሌለበት እቃ ወይም ግጣም በሌለበት ማጠጫ በኩል ከዚያ በሽታ ላይ  አንዳች በሽታ ሳያወርደበት አያልፍም፡፡” ሲሉ ሰምቻለሁ፡፡›› ብለዋል፡፡ ሙስሊም በቁጥር (2014) ላይ የዘገቡት ሲሆን ቡኻሪ ከጃቢር -አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው- በዘገቡት ሐዲሥ ላይ እንዲሁ፣ “አኮሌያችሁንም ግጠሙ፡፡ የአላህን ስምንም አውሱ፡፡ እቃዎቻችሁንም ሸፍኑ፡፡ የአላህንም ስም አውሱ፡፡ አንዳች ነገር በእሷ ላይ ብታጋድሙም፡፡” ብለዋል፡፡ ቡኻሪ በቁጥር (5623) ላይ ዘግበውታል፡፡

 

 
Simple Audio Player
 
facebook googleplus twitter